+25111681

ባህል እና ትምህርት፡- ሥነትምህርታዊ ዲስኩር ትንታኔ በተመረጡ የደብረብርሃን ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች

Kebede Yimer
Department of English Language and Literature, Debre Berhan University, P.O. Box 445, Debre Berhan, Ethiopia

Abstract

የዚህ ጥናት ዓላማ 9 ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የመማር እና የማስተማር መስተጋብር ላይ ከሥነትምህርታዊ ዲስኩር አኳያ ትንተና ማድረግ ነው፡፡ ይህን ዓላማ ለማሳካት በደብረብርሃን ከተማ በሚገኙ አራት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስድስት 9 ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መምህራን በአመቺ የንሞና ዘዴ በመምረጥ በክፍል ውስጥ ሲያስተምሩ በድምፅ እና ምሥል መቅረጫ አማካኝነት 18 ክፍለጊዜ መረጃ ተሰብስቧል፤ ተቀረጿል፡፡ መረጃው ወደ ምዝግብ መረጃነት ከተቀየረ በኋላም በንግግር ልውውጥ ትንተና ዘዴ መሠረት ተተንትኗል፡፡ የትንተናው ውጤትም የማስተናበሪያ እና የማስተማሪያ ዲስኩሮች የአወቃቀር ሥርዓት የአቃፊ እና የታቃፊ ቅንጅት እንደሆነ አመልክቷል፡፡ ይህም የማስተናበሪያ ዲስኩር አቃፊ ሲሆን የማስተማሪያ ዲስኩር ታቃፊ መሆኑን አሳይቷ፡፡ ነገር ግን የማስተናበሪያ ዲስኩር አቃፊ ሊሆን የሚችለው በእርእሰ ጉዳዩ መቋጫ ላይ ሲከሰት ነው፡፡ ከአገልግሎት አኳያም የማስተናበሪያ ዲስኩር የማስተማሪያ ዲስኩር በተቀላጠፈ መልኩ ይካሄድ ዘንድ እገዛ አደርጓል፡፡ በተጓዳኝ የማስተማሪ ዲስኩር የቋንቋ ትምህርቱ ማቅረቢ ሚዲያ በመሆን አገልግሏል፡፡ ስለዚህ መምህሩ በሚያስተምረው የትምህርት ዓይነት ላይ ያለውን ብቃት ለመገምግም መተኮር ያለበት በማስተማሪያ ዲስኩሩ ላይ ነው፡፡ ነገር ግን በክፍል አመራር ችሎታው ላይ ከሆነ በማስተናበሪያ ዲስኩሩ ላይ መሆን እንዳለበት ይህ ጥናት ይጠቁማል፡፡

Keywords: ትምህርታዊ ዲስኩር፣ የማስተናበሪያ ዲስኩር፣ የማስተማሪያ ዲስኩር፣ የንግግር ልውውጥ

Author Biographies

Kebede Yimer, Department of English Language and Literature, Debre Berhan University, P.O. Box 445, Debre Berhan, Ethiopia

Cover photo

Published:

2025-10-10

How to Cite


Issue:

2025-10-10